top of page

ሰለስቱ ፤ ወደራስ ጉዞ


ተመክሬ ነበር ፣ ስኬት እንድሰፍር ወዳጅ እንዳኮራ ፣ ጠላት እንዳሳፍር የህይወቴን እርሻ ፣ ላዳብር ላለማ እሰው ዘንድ ስፈትሽ ከዐለም ጓዳ ስሻ ከእንደኔው ሰባራ የፈራጅ ደንባራ

ስኳትን ከርሜ ፣ ውስጥ እግሬ ቢደማ ባጣው ውስጤ ገባሁ መሄጃ ቢጠፋኝ፣ ከኔው ጋር ተግባባሁ፧ ይዤው መባከኔን ልቤ መች አወቀ ፍፁምነት ዕንቊው፣ ማንም በማይዘርፈው ሹፈትን በናቀ፣ ሓሴታዊ አልማዝ እንዳሸበረቀ እውስጤ አገኘሁት፣ እጉድለቴ መሀል እንደተደበቀ።

#ethiopianwriter #Ethiopianpoetry #amharicpoetry #amharic

299 views0 comments

Recent Posts

See All
bottom of page